የሴቶችን የኢኮኖሚ አቅም ለማሻሻል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ

ጥር 7 /2018 የሳንኩራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን‎
‎በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት በሴቶች ልማት ህብረት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸምን በስትሪንግ ኮሚቴ ገምግሟል።
 
‎በተካሄደው መድረኩ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ታቅደው የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት አፈጻጸም ሪፖርት በሳንኩራ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ በወ/ሮ ዘይንያ ሸ/አደም በኩል ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
‎የሴቶችን የኢኮኖሚ አቅም ለማሻሻል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱን የገለፁት ወ/ሮ ዘይንያ በተሰሩ ስራዎችም በየደረጃው የሚገኙ ሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሻሻል እየተቻለ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡
‎ሴቶች የገቢ አቅማቸውን ለማሳደግ የተለያዩ የተሻሻለ የእንቁላል ዶሮዎችን ፣ የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያዎችን መጠቀም እንዲችሉ የማድረግ ፣ በሌማት ትሩፋት እና የቁጠባ ባህላቸውን ማሳደግ እንዲችሉ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ዋና ሀላፊዋ አስረድተዋል ፡፡
‎ወ/ሮ ዘይንያ አያይዘውም ፤ በወረዳው በሁሉም ቀበሌዎች ጽዱና ማራኪ አካባቢ መፍጠር ፣ ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ያለ-እድሜ ጋብቻ ማስቀረት ፣ በጎልማሶች ትምህርት ፣ በግብር ፣ በጤናና በትምህርት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎችም የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተቀናጅቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
‎በተለያዩ ጊዜያቶች የሚሰጡ ስልጠናዎች የሴቶችን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ያስረዱት ሀላፊዋ ስትሪንግ ኮሚቴው በየተቋሙ የሚሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደሆኑ ከተቋማት ፎካሎች ጋር ተቀራርቦ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
‎በመድረኩ ላይ በቀረበው ሰነድ መነሻ በማድረግ የወረዳው የስትሪንግ ኮሚቴው የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት ለማጎልበት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊና ፖለቲዊ ዘርፎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ሃሳብ አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
‎የውይይት መድረኩ በሳንኩራ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ በወ/ሮ ዘይንያ ሸ/አደም እና በሳንኩራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አቶ አርጋ ከድር የተመራ ነው፡፡
‎በመድረኩ የባለድርሻ ተቋማት ሀላፊዎች፤ የሴክተር መስሪያ ቤት ፎካሎች ፣ የተቋሙ የማኔጅመንት አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
👉ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ይከታተላሉ፣ይወዳጁ👇👇
‎➭የፌስቡክ Link፦ https://www.facebook.com/SWCTCAffairs
‎➪ዌብሳይት:-https://sankuraadmin.gov.et/
‎➭የቴሌግራም Link፦

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top